VATICAN-NEWS:
እዚህ እናነባለን፦
ወደ ኢየሩሳሌም እና የቤዛነት ኢዮቤልዩ መመልከት
እ.ኤ.አ. በ2033 የኢየሱስን ሕማማት፣ ሞት እና ትንሣኤ 2,000ኛ ዓመት የምስረታ በዓል - ለማክበር ወደ ቤዛነት ኢዮቤልዩ - ወደሚወስደው መንፈሳዊ መንገድ ላይ ሁሉም ሰው እንዲጓዝ የጋበዙ ቅዱስነታቸው ወደ ኢየሩሳሌም ለመመለስ በማሰብ፣ ኢየሱስ በመጨረሻው እራት የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበበት እና በኋላም በጴንጤቆስጤ ዕለት መንፈስ ቅዱስን የላከበት የላይኛው ክፍል እንደሚገኙ ያላቸውን ተስፋ ቅዱስነታቸው ገልጸዋል። ይህ ጉዞ ወደ ሙሉ አንድነት የሚያመራ ጉዞ ነው ሲሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ “በአንድነት አንድ ነን” የሚለውን መፈክር አስታውሰዋል።